image
image
image
image
image

ህጋዊ የደረሰኝ ግብይት በማስፈን የተረጋጋ የገበያ ሁኔታ ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ፡፡

ሀምሌ 2, 2017
የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የገበያ ማረጋጋት የጋራ ግብረ-ሃይል የተረጋጋ ገበያ ከመፍጠር አንፃር እንዲሁም ከደረሰኝ ቁጥጥር እና ክትትል ጋር እየተሰራ ያለውን ስራ ገምግሟል:: በመድረኩ የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ፣ የንግድ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አብዱልዋሂድ በድሩ፣ የሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ሃላፊ ዶ/ር ጥበቡ ደጀኔ እንዲሁም ሌሎች የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል:: የደረሰኝ ቁጥጥርና ክትትል ስራውን በማጠናከር ህጋዊ ግብይት ማስፈን እንደሚገባ የገለፁት የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ እና የጋራ ግብረሃይሉ ሰብሳቢ አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ የኑሮ ውድነቱን በማቃለል የተረጋጋ የገበያ ሁኔታ ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

መልዕክትዎን ይላኩ