image
image
image
image
image

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ አስተዳደር ወቅታዊ የፀጥታ ሥራዎች ያሉበት ደረጃ ተገመገመ::

ህዳር 16, 2017
መድረኩን የመሩት የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ምክትልና ፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ አቶ አብነት አሰግድ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የፀጥታ ስራ በመሰራቱ ሰላምና ደህንነቱ የተረጋገጠበት ክፍለ ከተማን መፍጠር መቻሉን ገልፀው ህዝባችንን ያሳተፈው የፀጥታ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ብለዋል:: የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ደመቀ ዋኘው በበኩላቸው ወንጀሎች ከመከሰታቸው በፊት የፀጥታ አዝማሚያና ዝንባሌዎችን በመቃኝት የአፍራሽ ኃይሉን እኩይ ተግባር አስቀድሞ በማክሸፍ አስተማማኝ ሰላም መረጠ ተችሏል ብለዋል:: የክፍለ ከተማው ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ሃላፊ ዶ/ር ጥበቡ ደጀኔ በበኩላቸው የፀጥታ ጥምር ኃይሉ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በቅንጅት በመስራት የክፍለ ከተማችንን ሰላምና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ መጠበቅ እና ህዝቡ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴው ተረጋግቶ እንዲኖር ማድረግ መቻሉን አስታውቀዋል::

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች